Leave a comment

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝብ በፅናት ይታገል!!!!


ከአጎ አሺሎ

38023561_282102385890705_1514103197361242112_nበኢትዮጵያ ታሪክ በራሱ መንግስታዊ አወቃቀር የተደራጀ በባህል በሀይማኖት ሳይለያይ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፍ ትልቅ ሚና የነበረው ይህ ታላቅ ሕዝብ በወያኔ /ኢህአዴግ አገዛዝ በሁለንተናዊ መንገድ ከፍተኛ ቀውስ የደረሰበት መሆኑ ይታወቃል ።
ይሁን እንጂ ገና ከ1983 አም ጀምሮ ሕልናውን ለመጠበቅ በፓለቲካ ፖርቲ ተደራጅቶ በኢትዮጵያ ውስጥ መንቀሳቀስ ብሞከርም የሕዝቡን የመደራጀት መብት በማፈን ብዙ የክልሉ ተወላጆች ከአገር እንዲሰደዱና ለተለያየ እንግልት ተዳረገዋል
በየትኛውም አገር እና አምባገነኖች ስረዐት የሕዝብን መብት ለማፈን አቅም እንደማይኖራቸው የሚታወቅ ሲሆን ጀግና የምዕራብ ኢትዮጵያ አከባቢ ተወላጆች በአገረ አሜርካ እንደ እ. ኤ.አ በ2016 የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝብ ህብረት
አቋቁመው ከፍተኛ ትግል ሲያደርጉ ቆይቷል። በአገራችን በዶክተር አብይ በተጀመረው ለውጥ በተለያዩ አገር የሚንቀሳቀሱ ፖርቲዎች አገር ውስጥ ገብተው እንድታገሉ በተጋበዙት መሠረት የደምኢሕህ ፖርቲ አባልና አመራር ተጋብዘው አገር ውስጥ መግባቱ ይታወቃል ።
ለስላም ለዴሞክራሲ ስርዐት ግንባታ ትላልቅና ወሳኝ አጀንዳዎችን ይዞ የሚንቀሳቀስ ፖርቲ በመሆኑ የፓርቲው አመራሮች አገር ውስጥ ገብተው በዋና ዋና የክልሉ ከተሞች ሕዝቡን ካወያዮ በኃላ የፓርቲውን አወቃቀር እና አደረጃጀት በመተከል ስራ ላይ የተጠመዱ በመሆኑ በአገሪቱ ሕግ መሠረት ከማንኛውም ፖለቲካ ፖርቲ ቀድሞ ከኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና ማግኘታቸው ይታወቃል ።
ፓርቲው ከክልሉ በተጨማሪ ተወላጆች ባሉበት ቦታ መዋቅሩን እያደራጀ ይገኛል ።በዚሁ መሠረት በአዲስአበባ የሚገኝ የቅርንጫፍ ፅ/ቤት ቀጣይና ተከታታይነት ያለው ግኑኘት እያደረጉ እና በቀጣይ የሚኖሩ ስራዎችንና በተለይ በ2012 የሚካሄደው ምርጫን እና አጠቃላይ የፓርቲው ፕሮግራሞችን ባካተተ መልኩ የምርጫ ማንፈስቶ አዘጋጅቶ ከተወያየ በኃላ በፓርቲው ጉባኤ አፀድቆ ወደ ከሕዝብ ጋሪ ለመወያየት ዕቅድ ላይ ይገኛል።
የተከበራችሁ በክልል ከክልሉ ውጭ እና ከአገር ውጭ የምትኖሩ አባላት ደጋፊዎች እና ሕዝባችን በክልላችን የምናደርገው ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፍትህ ለማረጋገጥ በመሆኑ የተሻለ ስርዐት እና ሰላም ለማስፈን የሁሉንም ድርሻ የሚጠይቅ እንደሆነ ፓርቲያችን ደምኢሕህ ስለሚያሚን ሁሉም የባለድርሻ አካል ከጎኑ እንዲቀም ጥሪውን ያቀርባል ።

“የተደራጀ ሕዝባዊ ትግል ለዴሞክራሲዊ ስረዐት!”

Leave a comment